28 lines
2.5 KiB
Markdown
28 lines
2.5 KiB
Markdown
# ነነዌ እንደሚያፈስ የኩሬ ውሃ ናት፣ ሕዝቧም እንደ ውሃ ፈሳሽ ይሸሻል
|
|
|
|
ናሆም ሕዝቡ ከነነዌ ከተማ የሚሸሽበትን ሁኔታ ግድብ በሚፈርስበት ጊዜ ውሃው ከማከማቻው ጎርፎ ከመውረዱ ጋር ያነጻጽረዋል። (ተነጻጻሪ የሚለውን ተመልከት)
|
|
|
|
# ብሯን በዝብዙ. . . የነነዌን የተዋቡ ነገሮች
|
|
|
|
እዚህ ጋ ተናጋሪው ማን እንደሆነ ግልጽ አይደለም። ይህ ምናልባት ናሆም ለተዋጊዎቹ አቅጣጫ የሚሰጥበት ይሆን ይሆናል ወይም ምናልባት ተዋጊዎቹ ለእርስ በእርሳቸው አቅጣጫ የሚሰጡበትና የሚነጋገሩበት ሊሆን ይችላል። (ምናባዊውን ሰው መናገር የሚለውን ተመልከት)
|
|
|
|
# ብሩን በዝብዙ፣ ወርቁን በዝብዙ
|
|
|
|
“በዝብዙ” የሚለው ቃል በማስገደድ የሚሰረቁ ነገሮች፣ አብዛኛውን ጊዜ በጦርነት ወቅት ማለት ነው። አ.ት፡ “ብሩን በብዝበዛ ውሰዱ፣ ወርቁን በብዝበዛ ውሰዱ” ወይም ”ብሩን ውሰዱ፣ ወርቁን ውሰዱ”
|
|
|
|
# ለእርሱም ማብቂያ የለውም
|
|
|
|
“ማብቂያ የለውም” የሚሉት ቃላት አንድ ነገር በብዛት መኖሩን ለመግለጽ የተነገረ ግነት ነው። አ.ት፡ “እጅግ ብዙ አለ” (ግነት እና ማጠቃለያ የሚሉትን ተመልከት)
|
|
|
|
# የነነዌ የተዋቡ ነገሮች ክብር ሁሉ
|
|
|
|
ይህ ሐረግ በነነዌ የነበረውን ብር፣ ወርቅ፣ እና ሌሎች ሀብቶች ያመለክታል። ግሱ ምናልባት ቀደም ካለው ሐረግ ሊወሰድ ይችላል። አ.ት፡ “ለነነዌ የተዋበ ሀብት ሁሉ ለክብሩ ማብቂያ የለውም” ( መግደፍ የሚለውን ተመልከት)
|
|
|
|
# የእያንዳንዱ ልብ ይቀልጣል
|
|
|
|
ናሆም ልክ ልባቸው እንደ ሰም የቀለጠ ይመስል ሕዝቡ አቅም እንዳጣ ይናገራል። አ.ት፡ “እያንዳንዱ አቅም አጥቷል” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)
|
|
|
|
# የእያንዳንዱ ጉልበት ይብረከረካል
|
|
|
|
ይህ በታላቅ ፍርሃት ምክንያት የሚፈጠረውን አካላዊ ምላሽ ያሳያል። የሕዝቡ እግር ያለ መጠን በመንቀጥቀጡ ጉልበቶቻቸው ስለሚጋጩ መራመድም ሆነ መሮጥ አይችሉም።
|