am_tn/lev/16/17.md

1.4 KiB

በእግዚአብሔር ፊት ወዳለው መሠዊያ ይምጣ

ይህ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ የሚገኝ የመሥዋዕት መሠዊያ ነው

ለመሠዊያው ያስተሠርይለት

እንደ ቅዱስ ቦታና መገናኛ ድንኳን መሠዊያው ከሰዎች ኃጢአት የተነሣ ርኩስ ይሆናል

የመሠዊያው ቀንዶች

በመሠዊያው ማዕዘናት ያሉ ቅርጾች ይህም የመሠዊያው ማዕዘናት ያመለክታል:: እንደ በሬ ቀንዶች የተቀረጹ ናቸው:: በዘሌዋዊያን 4:7 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ::

ለማንጻት

ለእግዚአብሔር ዓላማዎች መጠቀሚያ የሚገባው መሠዊያ ንጹህ እንደሆነ ተገልጾአል:: (ዘይቤያዊ አገላለጽ ይመልከቱ)

ለእግዚአብሔርም ይለዩት ከእስራኤልም ሕዝብ ርኩስ ተግባራት ያርቁት

ለእግዚአብሔር የተለየው መሠዊያ ከሕዝቡም ኃጢአት አንደተለየ ተደርጐ ተነግሮአል:: (ዘይቤያዊ አገላለጽ ይመልከቱ)

ርኩስ ድርጊቶች

በእግዚአብሔር ፊት ሰዎች ተቀባይነት እንዳይኖራቸው የሚያደርጉ ኃጢአታዊ ድርጊቶች ርኩስ ድርጊቶች ተብለው ተነግረዋል:: (ዘይቤያዊ አገላለጽ ይመልከቱ)