am_tn/job/38/14.md

1.9 KiB

ከማህተም በታች እንዳለ ጭቃ/ሸክላ የምድር መልኳ ይለወጣል

በምሽት፣ ሰዎች በግልጽ መመልከቱ አይችሉም፣ ማለዳ ግን ማህተም በሸክላ ላይ ግልጽ ምስልን እንደሚፈጥር ብርሃን የሁሉንም ነገር ቅርጽ በግልጽ መለየት ያስችላል፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

እንደ ቁራጭ ጨርቅ እጥፋት በእርሷ ላይ የሚገኙ ነገሮች ሁሉ በግልጽ ይታያል

እዚህ ስፍራ "እርሷ" የሚለው የሚያመለክተው ምድርን ነው፡፡ ይህ ሀረግ በዚህ ስንኝ ከሚገኘው የመጀመሪያው ሀረግ ጋር ተመሳሳይ ትርጉም አለው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ እና ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

ከክፉ ሰዎች "ብርሃናቸው" ይወሰዳል

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ማለዳ የክፉ ሰዎችን ‘ብርሃን' ይወሰዳል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

የእነርሱን ‘ብርሃን'

ክፉዎች ጨለማን ብርሃናቸው አድርገው ይቆጥራሉ፣ ምክንያቱም ክፉ ስራቸውን ሚሰሩት በጨለማ ሲሆን ደግሞም ከጨለማ ጋር ቅርርብ አላቸው፡፡ (ምፀት የሚለውን ይመልከቱ)

የተነሳው ክንዳቸው ይሰበራል

የተነሳው የክፉዎች እጅ የሚለው የሚወክለው ሀይላቸውን እና ክፉ ለማድረግ ያላቸውን ፍላጎት ነው፡፡ ነገር ግን የማለዳው ብርሃን ስወጣ ክፉዎች እነዚያን ክፉ ነገሮች ማድረጋቸውን ያቆማሉ፡፡ (ዘይቤያው አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)