28 lines
1.7 KiB
Markdown
28 lines
1.7 KiB
Markdown
# የእስራኤል አምላክ
|
|
|
|
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጎሞች፡- 1) የእስራኤልን አምላክ መደበኛ ስም እየጠሩ ነበር ወይም 2) "የእስራኤል አምላክ'፣ እስራኤል ከብዙ አማልክት መካከል አንዱን ያመልኩ እንደነበር ያምኑ ነበር፡፡ 1ሳሙኤል 5፡7 እንዴት እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡
|
|
|
|
# የበደል መሥዋዕት መልሱለት እንጂ ባዶውን አትስደዱት
|
|
|
|
ባዶውን አትስደዱት የሚሉት ቃላት አንድን ነገር አጠንክሮ መናገሪያ መንገድ ናቸው፡፡ አት፡- "የበደል መሥዋዕት መስደድ አለባችሁ' (ፈሊጣዊ ንግግር ተመልከት)
|
|
|
|
# ትፈወሳላችሁ
|
|
|
|
"ከእንግዲህ ወዲህ አትታመሙ'
|
|
|
|
# እናንተ
|
|
|
|
እናንተ የሚለው ተውላጠ ስም የብዙ ቁጥር እንደመሆኑ ፍልስጥኤማውያንን ሁሉ ያመለክታል፡፡ (አንተ/እናንተ ተመልከት)
|
|
|
|
# እጁ ከእናንተ አለመራቁ ስለምን ነው
|
|
|
|
በዚህ ስፍራ "እጅ' የሚለው ቃል እግዚአብሔር መከራን ለማምጣትና ለመቅጣት ያለውን ኃይል ለመግለጽ ጥቅም ላይ የዋለ ምትክ ቃል ነው፡፡ አት፡- "መከራችሁን ለምን አላቀለላችሁም' (ምትክ ቃል ተመልከት)
|
|
|
|
# እጢ
|
|
|
|
ሊሆኑ የሚችሉ ትርጎሞች፡- 1) ከቆዳ ስር የሚወጣ የሚያሰቃይ እባጭ ወይም 2) የአህያ ኪንታሮት 1ሳሙኤል 5፡6ን እንዴት እንደተረጎምክ ተመልከት፡፡
|
|
|
|
# አይጦች
|
|
|
|
ከአንድ በላይ አይጥ
|