am_tn/psa/074/018.md

28 lines
1.9 KiB
Markdown
Raw Permalink Normal View History

2021-03-06 16:01:31 +00:00
# አጠቃላይ መረጃ፡-
አሳፍ የእግዚአብሔርን እርዳታ እየጠየቀ ነው፡፡
# አስብ
“ትኩረት ስጥ፡፡” ይህ በ መዝሙረ ዳዊት 74:2 ላይ እንዴት እንደተተረጎመ ተመልከት፡፡ (ፈሊጥ የሚለውን ይመልከቱ)
# ጠላት በአንተ ላይ ስድብን አወረደ
አሳፍ ስለ ስድብ ቃላቶች ሲናገር ጠላት በእግዚአብሔር እንደሚወረውረው እንደ ድንጋይ ቁሳዊ ነገር እንደሆነ ተደርጎ ተገልጧል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ጠላት አንተን ብዙ ጊዜ ሰደበህ” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
# የርግብህን ህይወት
አሳፍ ስለ ራሱ ማንም ረዳት እንደሌላት ወፍ እንደ ርግብ አድርጎ ተናግሯል፡፡ ይህ ሀረግ ለእስራኤል ህዝብ ምናልባት ተለዋጭ ዘይቤ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እኔ፣ የአንተ ርግብ” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
# ርግብ
ራስዋን መከላከል የማትችልና እንደ ለማዳ እንስሳ የምትጠበቅ ትንሽ ወፍ ናት፡፡
# የዱር እንስሳ
ይህ ምናልባት ለእስራኤል ጠላት ተለዋጭ ዘይቤ ሊሆን ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እንደ ዱር እንስሳ የመሰለ ጨካኝ ጠላት” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)
# የችግረኞች ህዝብህን ህይወት ለዘላለሙ አትርሳ
“የተቸገሩ ህዝብህን ለመርዳት ምንም ነገር ካለማድረግ ለዘላለል አትቀጥል፡፡” ይህ በአዎንታዊ ቅርፅ ሊብራራ ይችላል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የተቸገሩ ህዝብህን ለመርዳት በፍጥነት ና” (ምፀት የሚለውን ይመልከቱ)