Wed Jul 05 2017 22:39:54 GMT+0300 (E. Africa Standard Time)
This commit is contained in:
parent
93b683cda2
commit
d21f153a2d
|
@ -0,0 +1,3 @@
|
|||
\v 15 \v 16 \v 17 15. አስፈሪ ነገሮች እየሆነብን ነው! ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ እግዚአብሔር ተጨማሪ ጥፋቶች እንዲደርሱብን በሚያደርግበት ጊዜ እኛን የሚቀጣበት ወቅት ፈጥኖ ይደርሳል፡፡
|
||||
16. ሰብሎቻችን ቀደም ብለው ጠፍተዋል፤ በአምላካችን ቤተ መቅደስም አንድም ሰው ጨርሶ ሐሤት አያደርግም፡፡
|
||||
17. ዘርን ስንዘራ አይበቅልም፤ በመሬት ውስጥ ይደርቃል፤ ስለዚህ የምንሰበስበው ሰብል የለንም፤ ጐተራዎቻችን ባዶ ናቸው፤ በእነርሱ ውስጥ የምናከማቸው እህል የለንም፡፡
|
|
@ -0,0 +1,3 @@
|
|||
\v 18 \v 19 \v 20 18. ጥቂት የሚበላ ሣር ያለበትን መሰማሪያ በመፈለግ ከብቶቻችን ያቃስታሉ፤ እየተሠቃዩ በመሆናቸው በጎቹም ይጮኻሉ፡፡
|
||||
19. ማሰማሪያዎቻችንና ደኖቻችን ደርቀዋልና እግዚአብሔር ወደ አንተ እጮኻለሁ፡፡
|
||||
20. ወንዞቹ ሁሉ ደርቀዋልና የዱር እንስሳቱ እንኳ ወደ አንተ እንደሚጮኹ ናቸው፤ ድርቀቱ የምድረ በዳውን ማሰማሪያዎች እንደሚያቃጥል የሚነድ እሳት ነው፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\c 2 \v 1 \v 2 1. በእግዚአብሔር የተቀደሰ ተራራ በኢየሩሳሌም ባለው የጽዮን ተራራ መለከትን ንፉ! እግዚአብሔር እኛን በተጨማሪ የሚቀጣበት ጊዜ ፈጥኖ ስለሚደርስ መፍራትና መንቀጥቀጥ እንዳለባቸው ለይሁዳ ሕዝብ ተናገር፡፡
|
||||
2. ያ ቀን እጅግ ጨለማና ጭጋጋማ ቀን ነው፤ ጥቁር ደመና ስለሚኖር እጅግ ጨለማ ነው፤ ግዙፍ የአንበጣ መንጋ ተራራውን ስለሸፈነው እንደ ጥቁር ደመና ይሆናል፤ እንደዚህ ያለ ነገር ከዚህ ቀደም በፍጹም አልሆነም፤ እንደዚህ ያለ ነገር በፍጹም ዳግመኛ አይሆንም፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 3 3. ማንም ሊያመልጠው የማይችል የእሳት ነበልባል ያመጡ ያህል ነው፤ በፊታቸው ምድሪቱ እንደ ዔደን ገነት የተዋበች ነች፤ በስተኋላቸው ግን ምድሪቱ እንደ በረሐ ነች፤ ምንም ነገር በሕይወት አይኖርም፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 4 \v 5 4. አንበጦቹ ፈረሶችን ይመሳስላሉ፤ በፈረሶች ላይ እንደተቀመጡ ወታደሮችም ይጋልባሉ፡፡
|
||||
5. ለጦርነት እንደሚዘጋጅ ኃያል ሠራዊት ወይም በሜዳ ላይ ገለባን የሚያቃጥል እሳት እንደሚያሰማው ፉጨት በተራሮች ጫፍ ላይ ሲዘሉ የሰረገሎችን የማንኳኳት ድምፅ የመሰለ ድምፅ ያሰማሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 6 \v 7 6. ሰዎች መምጣታቸውን ሲመለከቱ እጅግ ይገረጣሉ ይፈሩማል፡፡
|
||||
7. ወታደሮች እንደሚያደርጉት አንበጦቹ በግድግዳዎች ላይ ይዘላሉ፤ ረድፋቸውንም ጠብቀው ይጓዛሉ እንጂ በፍጹም ከመስመራቸው ዝንፍ አይሉም (አይወጡም)፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 8 \v 9 8. እርስ በርሳቸው ሳይጋፉ ወደፊት ይገሠግሣሉ፤ ሰዎች ጦርና አንካሴ ቢወረውሩባቸውም ያ እንዲቆሙ አያደርጋቸውም፡፡
|
||||
9. በከተማ ቅጥሮች ላይ ይርመሰመሳሉ ወደ ቤቶቻችንም ይገባሉ፤ ሌቦች እንደሚያደርጉት በመስኮቶቻችን በኩል ይገባሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 10 \v 11 10. መሬት እንድትንገዳገድ ሰማይም እንዲንቀጠቀጥ እንደሚያደርጉ ያህል ነው፡፡ በሰማዩ ላይ እጅግ ብዙ አንበጦች ስለሚኖሩ ፀሐይና ጨረቃ ይጨልማሉ፤ ክዋክብትም አያንፀባርቁም፡፡
|
||||
11. ሊቈጠር የማይችለውን ይህንን የአንበጣ ሠራዊት እግዚአብሔር ይመራዋል፤ እነርሱም የእርሱን ትእዛዝ ያከብራሉ፤ ማንም በሕይወት ሊተርፍ የሚችል እስከማይመስል ድረስ ይህ አሁን በእኛ ላይ የሚፈርድበትና እኛን የሚቀጣበት ጊዜ እጅግ አስፈሪ ነው፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 12 \v 13 12. እግዚአብሔር ግን እንደዚህ ይላል፡- ‹‹እንደደረሱባችሁ እንደነዚህ ጥፋቶች ሳይሆን በመላ ውስጣዊ ማንነታችሁ እናንተ ወደ እኔ መመለስ ትችላላችሁ፤ እኔን በመተዋችሁ እንዳዘናችሁ ለማሳየት አልቅሱ፣ ዋይ በሉ ደግሞም ጹሙ፡፡
|
||||
13. ማዘናችሁን ለመግለጽ ልብሶቻችሁን ብቻ አትቅደዱ፤ ከዚያ ይልቅ በውስጣዊ ማንነታችሁ ማዘናችሁን ግለጹ፡፡›› እግዚአብሔር መሐሪና ደግ ነው ፈጥኖ አይቈጣም፤ በታማኝነት ሕዝቡን ይወዳል፡፡ ፈጥኖ አይቆጣም፣ ከዚያ ይልቅ እጅግ አብዝቶና በታማኝነት ይወዳችኋል፤ እኛንም መቅጣት አይወድም፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 14 14. እናንተን ለመቅጣት የወሰነውን ውሳኔ ለውጦ በዚያ ፋንታ በምሕረቱ ያደርግላችሁ እንደሆነ ማንም አያውቅም፤ እንደዚያ የሚያደርግ ከሆነ ከሚሰጣችሁ ነገሮች ጥቂቱን ለእርሱ መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ እህልና ወይን አትረፍርፎ በመስጠት ይባርካችኋል፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 15 \v 16 15. በጽዮን ተራራ መለከትን ንፉ፤ ሕዝቡንም ሰብስቡ! ስለ ኃጢአታችሁ ማዘናችሁን ለመግለጽ የተለየ የጾም ወቅት ቅጠሩ፡፡
|
||||
16. በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት እንድታገኙ የሚያደርጓችሁን ሥርዓቶች ፈጽሙ፤ አዛውንቶቹና ልጆቹ ሕፃናቱም ሳይቀሩ፣ ሙሽሪርንና ሙሽራውን ለእልፍኞቻቸው (ከጫጉላ ቤታቸው) ጠርታችሁ ለየት ብላችሁ ለዓላማ እንደተሰለፈ ወገን በአንድት ተያያዙ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 17 17. እግዚአብሔርን የሚያገለግሉንም ካህናት በመሠዊያውና በቤተ መቅደሱ መካከል እንዲያለቅሱና እንደዚህም ብለው እንዲጸልዩ ንገሯቸው፡- ‹‹እግዚአብሔር ሆይ፣ እኛን ሕዝብህን አድነን፤ የባዕድ ሕዝቦች እንዲንቁን አትፍቀድላቸው፤ እንዲያፌዙብንና ‹‹አምላካቸው ለምን ተዋቸው?›› እንዲሉን አትፍቀድላቸው፡፡››
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 18 \v 19 18. እግዚአብሔር ግን ስለ ሕዝቡ ግድ እንደሚለውና ለእነርሱም በምሕረቱ እንደሚያደርግላቸው ዐሳየ፡፡
|
||||
19. ሕዝቡ ሲጸልይ እግዚአብሔር መለሰ እንዲህም አለ፡- ‹‹እኔ እህልና ወይን ጠጅ እንዲሁም የወይራ ዘይት አትረፍርፌ እሰጣችኋለሁ፤ እናንተም ትረካላችሁ፤ ባዕድን ሕዝቦችም እንዲሰድቧችሁ ከእንግዲህ አልፈቅድላቸውም፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 20 20. ሌላ የአንበጣ ሠራዊት እናንተን ለማጥቃት ከሰሜን ይመጣል፤ ነገር ግን ኢየሩሳሌምን አልፈው ወደ በረሐው ጉዟቸውን እንዲቀጥሉ አደርጋቸዋለሁ፤ አንዳንዶቹ በስተምሥራቅ በኩል ወደ ሙት ባሕር ይሄዳሉ፤ አንዳንዶቹ በስተምዕራብ በኩል ወደ ታለቁ ባሕር ይሄዳሉ፤ በዚያ ሁሉም ይሞታሉ፣ አካላቸውም ይከረፋል (ይገማል)፤ ለእናንተ ድንቅ ነገሮችን አደርግላችኋለሁ፡፡››
|
|
@ -0,0 +1,3 @@
|
|||
\v 21 \v 22 \v 23 21. በእርግጥም እግዚአብሔር ድንቅ ነገሮችን ያደርጋል፤ ስለዚህ ምድሪቱ እንኳን ደስ ሊላት ይገባል!
|
||||
22. መስኩ ፈጥኖ ይለመልማልና የዱር እንስሳቱ ሊፈሩ አይገባቸውም፤ በለሱና ሌሎቹ ዛፎች በፍሬ የተሞሉ ይሆናሉ፤ የወይን ተክሉም በዘለላዎች ይሸፈናል፡፡
|
||||
23. እናንተ የኢየሩሳሌም ሕዝብ ሆይ፣ እግዚአብሔር አምላካችሁ ስለሚያደርግላችሁ ነገር ደስ ይበላችሁ፤ እርሱ ከዚህ ቀደም ሲያደርግላችሁ እንደነበረው በወቅቱ በፀደይና በበልግ ወራት የተትረፈረፈን ዝናብ ይልክላችኋል፡፡
|
Loading…
Reference in New Issue