Sat Oct 13 2018 05:28:04 GMT+0300 (E. Africa Standard Time)
This commit is contained in:
parent
71f459274a
commit
19d93be37c
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 11 11. ያህዌም እንዲህ አለኝ፤
|
||||
\v 12 12. የምሳሌውን ትርጒም መረዳት ይችሉ እንደሁ እስቲ እነዚያን ዐመፀኞች ጠይቃቸው፤ የባቢሎን ንጉሥ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ንጉሡንና መሳፍንቱን ወደ ባቢሎን እንደ ወሰዳቸው ንገራቸው፤
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 13 13. ከዚያም ከንጉሥ የቅርብ ዘመዶች አንዱን ወስዶ አነገሠው፤ ለእርሱ ታማኝ እንዲሆንለትም ቃል አስገባው፡፡ የባቢሎን ንጉሥ ሌሎች የታወቁ የይሁዳ ሰዎችንም ወደ ባቢሎን ወሰደ፤
|
||||
\v 14 14. ይህንንም ያደረገው የይሁዳ መንግሥት ከእንግዲህ እንዳይነሣና ኃያል እንዳይሆን ነበር፡፡ የባቢሎን ንጉሥ ዕቅድ ሕዝቡ ለባቢሎን ንጉሥ የገባውን ቃል የማይጠብቅ እስከ ሆነ ድረስ፣ የይሁዳ መንግሥት ጨርሶ እንዲጠፋ ነበር፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 15 15. የባቢሎንን ሠራዊት መውጋት የሚችልበት ፈረሶችና ሰራዊት እንዲልክለት ወደ ግብፅ ባለ ሥልጣኖች መልእክተኞችን በመላክ የይሁዳ ንጉሥ የባቢሎን ንጉሥ ላይ ዐመፀ፤ ይህ ዕቅዱ ግን አልተሳካለትም፤ የገቡትን ውል የሚያፈርሱ ገዦች በፍጹም ማምለጥ አይችሉም፡፡
|
||||
\v 16 16. እኔ ጌታ ያህዌ በሕያውነቴ እምላለሁ፣ ይህ ንጉሥ በዙፋን ላይ ካስቀመጠው ከባቢሎን ንጉሥ ጋር በመሐላ የገባውን ቃል በማፍረሱ በባቢሎን ይሞታል፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 17 17. ባቢሎናውያን ብዙ ሰዎችን ለመግደል በከተማው ዙሪያ ቦይ ቆፍረው ዐፈር በመደልደል ምሽግ ስለሚሠሩ እጅግ ብዙ ሠራዊት ይዞ የሚመጣው የግብፅ ንጉሥ የይሁዳን ንጉሥ መርዳት አይችልም፡፡
|
||||
\v 18 18. የይሁዳ ንጉሥ መሐላውን በመናቅ ቃል ኪዳኑንም በማፍረስ፣ እጁን ከሰጠ በኃላ እርዳታ ለማግኘት ወደ ግብፅ ባለ ሥልጣኖች መልእክተኞች ልኮአልና ከባቢሎን ንጉሥ ቅጣት አያመልጥም፡፡
|
|
@ -0,0 +1,3 @@
|
|||
\v 19 19. ስለዚህ ጌታ ያህዌ እንዲህ ይላል፤ በሕያውነቴ እምላለሁ፤ ያቃለለውን መሐላዬንና ያፈረሰውን ኪዳኔን በራሱ ላይ አመጣለሁ፡፡
|
||||
\v 20 20. መረቤን በላዩ እዘረጋለሁ፤ በወጥመድም ይያዛል፤ ወደ ባቢሎን እወስደዋለሁ፤ በእኔ ላይ ስላመፀም በዚያ እፈርድበታለሁ፡፡
|
||||
\v 21 21. ማምለጥ የሞከረ ሰራዊቱ በጠላቶቻቸው ሰይፍ ይገደላሉ፤ በሕይወት የተረፉትም በተለያዩ አቅጣጫ ይበተናሉ፡፡ ያኔ እኔ ያህዌ የተናገርሁትን የማድረግ ሥልጣን እንዳለኝ ታውቃላችሁ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 23 \v 22 22. ጌታ ያህዌ እንዲህ ይላል፤ ከረጅሙ ዝግባ ጫፍ ላይ አንድ ቅርንጫፍ ወስጄ እተክለዋለሁ፤ ከቀንበጦቹ ጫፍ አንዱን ቀንጥሼ ከፍ ባለ ተራራ ላይ እተክለዋለሁ፡፡ ቅርንጫፎች ያወጣል፤ ፍሬ ያፈራል፤ ያማረ ዝግባም ይሆናል፡፡ የወፍ ዐይነት ሁሉ መኖሪያውን በዚያ ያደርጋል፤ በቅርንጫፎቹም ጥላ ሥር ያርፋል፡፡
|
Loading…
Reference in New Issue