Thu Jul 13 2017 11:46:39 GMT+0300 (E. Africa Standard Time)
This commit is contained in:
parent
09b2664440
commit
10bd70599b
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
7. እግዚአብሔር ሊያደርግ ያቀደውን ሁሉ ለነቢያቱ ይነግራቸዋል፡፡
|
||||
8. ማንኛውም ሰው አንበሳ ሲያገሳ በሚሰማበት ጊዜ በእርግጥ ይደነግጣል፤ እግዚአብሔር አምላክ ለነቢያቱ መልእክት ሰጥቷቸዋል፤ ምንም እንኳን ሰዎችን የሚያስደነግጡ ቢሆኑም እነርሱ በእርግጥ እነዚያን መልእክቶች ማወጅ ይገባቸዋል፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 9 \v 10 9. ለሰማርያ መሪዎች እንደዚህ አልኋቸው፡- በአሸዶድ፣ ከተማና በግብፅ ላሉ መሪዎች ይህንን መልእክት ላኩላቸው፡- ‹‹ወደ ሰማርያ ኮረብቶች ኑና መሪዎቻቸው በዚያች ከተማ ያሉ ሰዎች እንዴት እንዲደነግጡና እንዲሠቃዩ እንደሚያደርጉ ተመልከቱ!››
|
||||
10. በዚያ ያሉ ሰዎች ትክክለኛ የሆነውን ነገር እንዴት እንደሚያደርጉ አያውቁም ይላል እግዚአብሔር፤ ቤቶቻቸው ከሌሎች ሰዎች በሰረቋቸው ወይም በግፍ በቀሟቸው ውድ ነገሮች ተሞልተዋል፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
11. ስለዚህ እግዚአብሔር አምላካችን ጠላቶቻቸው ፈጥነው ይመጣሉ፣ መከላከያዎቻቸውን አፍርሰው እነዚያን ውድ ነገሮች ይወስዳሉ ይላል፡፡
|
||||
12. እግዚአብሔር እንደዚህ ብሏል፡- ‹‹አንበሳ በጎችን ሲያጠቃ እረኛ አንዳንድ ጊዜ ከአንበሳው አፍ የበጉን ሁለት እግሮች ወይም አንዱን ጆሮ ብቻ ማስጣል ይችላል፤ ከሰማርያም በተመሳሳይ ሁኔታ ጥቂት ሰዎች ብቻ ያመልጣሉ፤ እነርሱም የወንበር ስባሪና ከአልጋው ከፊሉን ብቻ ማስቀረት ይችላሉ››
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 13 \v 14 13. የሠራዊተ መላእክት አዛዥ እግዚአብሔር እንደዚህ ይላል፡- ‹‹ስለ ያዕቆብ ዝርያዎች ይህንን መልእክት አውጁ፡-
|
||||
14. በሠሯቸው ኃቲአቶች ምክንያት እኔ እግዚአብሔር የእስኤልን ሕዝብ ስቀጣ በቤቴል ከተማ ያሉት መሠዊያዎች እንዲፈርሱ አደርጋለሁ፤ በመሠዊያዎቹ ጥጎች ያሉት ማዕዘኖች እንኳን ተቈርጠው ወደ መሬት ይወድቃሉ፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 15 15. በክረምት የሚኖሩባቸውን ቤቶች እንዲፈርሱ አደርጋለሁ፤ የሚያማምሩ ትላልቅ ቤቶች እንደዚሁም በዝሆን ጥርስ የተጌጡ ቤቶች ይፈርሳሉ፤ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁና ይህ በእርግጥ ይፈጸማል!››
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\c 4 1. በባሳን አውራጃ እንዳሉ የሰቡ ላሞች እየወፈራችሁ ያላችሁ እናንተ ባለጠጋ የሰማርያ ሴቶች፣ ድኾችን ትጨቊናላችሁ፤ የተቸገሩ ሰዎችንም ታሠቃያላችሁ ለባሎቻችሁም፡- ‹‹የምንጠጣውን ብዙ ወይን ጠጅ አምጡልን!›› ትሏቸዋላችሁ፡፡
|
||||
2. ነገር ግን እግዚአብሔር አምላካችን እንደዚህ ብሏል፡- ‹‹እኔ ቅዱስ ነኝና ይህንን ተስፋ አስረግጬ እናገራለሁ፡- እናንተ ሁላችሁም ወደ ሌላ አገር የምትወሰዱበት ጊዜ ፈጥኖ ይደርሳል፣ ጠላቶቻችሁ እናንተን የሚይዙባቸው የተሳሉ መንጠቆዎችን እየተጠቀሙ፣ ይወስዷችኋል፡፡
|
|
@ -0,0 +1 @@
|
|||
\v 3 3. ጠላቶቻችሁ ጐትተው ያወጧችኋል፣ እናንተም በከተማይቱ ቅጥር ፍራሾች ለመሹለክ ትገደዳላችሁ፤ ወደ ሔርሞንም እንድትሄዱ ትገደዳላችሁ፡፡ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁና ይህ በእርግጥ ይፈጸማል!
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 4 \v 5 4. እኔን የሚያመልኩ ብዙ ሰዎች ወዳሉባቸው በቤቴልና በጌልጌላ ወዳሉ የኮረብታ ጫፍ የጣዖታት ማምለኪያ ስፍራዎች ተነሥታችሁ ሂዱ፤ በእኔ ላይም የምታደርጉትን ዓመፅ አብልጣችሁ ፈጽሙ እዚያም በደረሳችሁ በማግሥቱ መሥዋዕቶቻችሁን አቅርቡ፣ በማግሥቱም የእህላችሁን ዐሥራት አምጡልኝ፡፡
|
||||
5. ለእኔ ምስጋና ለማቅረብ የኅብስት መባዎችን እንደዚሁም ማቅረብ የሌለባችሁን ሌሎች መባዎችን አቅርቡ፤ ከዚያም ስላቀረባችኋቸው ስለ እነዚህ መባዎች በትምክህት ተናገሩ፤ ምክንያቱም ማድረግ የምትወዱት ይህንን ነውና፤ ይህንን የምታደርጉት ሌሎችን ለማስደነቅ ነው እንጂ እኔን ደስ ለማሰኘት አይደለም፤ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬዋለሁና ይህ በእርግጥ እውነት ነው፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 6 \v 7 6. በየትኞቹም ከተሞቻችሁና መንደሮቻችሁ ምግብ እንዳይኖ ያደረግሁት እኔ ነኝ፣ እንዲዚያ ባደርግባችሁም እናንተ ግን ተዋችሁኝ፡፡
|
||||
7. የእህሉን መከር ከመሰብሰባችሁ በፊት ገና ሦስት ወር ቀደም ብሎ፣ ሰብላችሁ ዝናብ እጅግ በሚያስፈልገው ወቅት ዝናብ እንዳይዘንብ ከለከልሁ፤ የአንዳንድ ጊዜ በአንዳንድ ከተሞች ዝናብ እንዲዘንብ ስፈቅድ በሌሎቹ ከተሞች ደግሞ እንዳይዘንብ ከለከልሁ፤ ዝናብ በአንዳንድ እርሻዎች ላይ ዘነበ፤ በሌሎች እርሻዎች ላይ ግን አልዘነበም፤ ከዚህም የተነሣ ዝናብ ባልዘነበባቸው እርሻዎች የነበረው መሬት ደረቀ፡፡
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 8 \v 9 8. ሰዎቻችሁ ውሃ ለማግኘት ከአንዱ ከተማ ወደ ሌላ ከተማ በመሄድ ይዘለፈለፋሉ፤ ሆኖም የሚጠጣ በቂ ውሃ እንኳን አያገኙም፤ እንደዚያ ቢሆንም እናንተ ግን ወደ እኔ አልተመለሳችሁም፡፡ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬዋለሁና ይህ በእርግጥ ይሆናል!
|
||||
9. የእህል እርሻዎቻችሁ እንዲደርቁ፣ የአትክልት ስፍራዎቻችሁና የወይን ተክሎቻችሁ በዋግ እንዲመቱ አደረግሁ፤ በበለስና በወይራ ዛፎቻችሁ ያሉትን ቅጠሎች የሚበሉ አንበጣዎችን ላክሁ፤ ይህንን ባደርግም እናንተ ግን ተዋችሁኝ፤ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬዋለሁና ይህ በእርግጥ ይፈጸማል!
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 10 \v 11 10. በግብፅ ሕዝብ ላይ እንደላክኋቸው ያሉ መቅሠፍቶች እንዲደርሱባችሁ አደረግሁ፤ ብዙ ወጣቶቻችሁ በጦርነት እንዲሞቱ አደረግሁ፤ ፈረሶቻችሁንም ጠላቶቻችሁ እንዲማርኳቸው ፈቀድሁ፤ ከወታደሮቻችሁ ብዙዎቹ ተገደሉ፤ ሰፈራችሁም በእነርሱ አስክሬን ጠረን ተሞላ፤ እንደዚህ ባደርግባችሁም እናንተ ግን እኔን ተዋችሁኝ፤ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬዋለሁና ይህ በእርግጥ ይፈጸማል!
|
||||
11. እንደ ሰዶም እንደ ገሞራ ሕዝብ ብዙዎቻችሁን አስወገድኋችሁ፤ ያልሞታችሁት እናንተ ጨርሶ እንዳይነድ ከእሳት ውስጥ እንደተነጠቀ ትንታግ ነበራችሁ፤ ይህንን ባደርግባችሁም እናንተ ግን ተዋችሁኝ፡፡ እኔ እግዚአብሔር ተናግሬዋለሁና ይህ በእርግጥ ይፈጸማል!
|
|
@ -0,0 +1,2 @@
|
|||
\v 12 \v 13 12. ስለዚህ አሁን እናንተ የእስራኤል ሕዝብ ሆይ እቀጣችኋለሁ፡፡ በእናንተ ላይ በምፈርድበት ጊዜ በእኔ በአምላካችሁ ፊት ለመቆም ተዘጋጁ!
|
||||
13. እኔ ተራሮችንና ነፋሳትን ፈጥሬአለሁ፤ ለሰው ልጆችም የማስበውን እገልጻለሁ፤ አንዳንድ ጊዜም የቀን ብርሃን እንደ ሌሊት ጨለማ እንዲሆን አደርጋለሁ፤ ማንኛውንም ነገር አዛለሁ፤ በምድር ላይ ባለው እጅግ ከፍተኛ ተራራ ላይ እንኳን እራመዳለሁ! እኔ እግዚአብሔር የሠራዊተ መላእክት አዛዥ ነኝ!››
|
Loading…
Reference in New Issue