am_act_text_ulb/25/23.txt

1 line
713 B
Plaintext

\v 23 ስለ ሆነም በማግስቱ አግሪጳና በርኒቄ በታላቅ ሥነ ሥርዓት ከወታደራዊ መኮንኖችና ከከተማዋ ታዋቂ ሰዎች ጋር ወደ አዳራሹ ገቡ። ፊስጦስም ባዘዘ ጊዜ ጳውሎስን ወደ እነርሱ አመጡት። \v 24 ፊስጦስም እንዲህ አለ፤ “ ንጉሥ አግሪጳ ሆይ፣ እዚህ ከዚህ ከእኛ ጋር ያላችሁም ሰዎች ሁሉ፣ ይህን ሰው ተመልከቱት፤ በኢየሩሳሌም እዚህም ደግሞ ያሉት የአይሁድ ሕዝብ ሁሉ ከእኔ ጋር ተማከሩ፤ ከእንግዲህ ወዲያ በሕይወት መኖር የለበትም ብለውም ጮኹብኝ።