9 lines
1.2 KiB
Markdown
9 lines
1.2 KiB
Markdown
# የጌታ ቀን፣ ይያህዌ ቀን
|
|
|
|
“የያህዌ ቀን” የተሰኘው የብሉይ ኪዳን አገላለጽ ከኀጢአታቸው የተነሣ እግዚአብሔር ሕዝቡን የሚቀጣበትን የተለየ ቀን ወይም ቀኖች ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል።
|
|
|
|
* “የጌታ ቀን” የሚለው የአዲስ ኪዳን አገላለጽ ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው በመጨረሻው ቀን ጌታ ኢየሱስ በሰዎች ለመፍረድ ተመልሶ የሚመጣበትን ቀን ነው።
|
|
* ይህ ወደ ፊት የሚመጣው የመጨረሻ ፍርድና ትንሣኤ አንዳንድ ጊዜ፣ “የመጨረሻው ቀን” ተብሎ ይጠራል። ይህ ጊዜ የሚጀምረው በኀጢአተኞች ለመፍረድና ለዘላለም መንግሥቱን ለመምሥረት ጌታ ኢየሱስ ሲመታ ነው።
|
|
* እነዚህ ሐረጎች ውስጥ፣ “ቀን” የሚለው ቃል አንዳንዴ ቃል በቃል “ጊዜን” ወይም ከቀን የረዘመ “ወቅትን” ሊያመለክት ይችላል።
|
|
* የቅጣቱ ቀን አንዳንዴ፣ “የእግዚአብሔር ቍጣ መፍሰስ” ተብሎ ይጠራል።
|