12 lines
1.9 KiB
Markdown
12 lines
1.9 KiB
Markdown
# መጥራት፣ ጥሪ፣ ተጠራ፣ መጣራት
|
|
|
|
“መጥራት” እና “መጣራት” የተሰኙ ቃሎች ቅርብ ላልነበረ ሰው ጮኽ ብሎ አንዳች ነገር መናገር ማለት ነው። ሌሎች ምሳሌያዊ ትርጕሞችም አሏቸው።
|
|
|
|
* አንድን ሰው “መጣራት” ሩቅ ላለ ሰው ጮኽ ብሎ መናገር ማለት ሲሆን፣ ርዳታ መጠየቅ፣ በተለይም የእግዚአብሔርን ርዳታ መጠየቅ ማለትም ይሆናል።
|
|
* ብዙውን ጊዜ መጽሕፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “መጥራት” ሲባል፣ “ና ማለት” ወይም፣ “እንዲመጣ ማዘዝ” ወይም፣ “እንዲመጣ መጠየቅ” ማለት ነው።
|
|
* ሕዝቡ እንዲሆኑ ወደ እርሱ እንዲመጡ እግዚአብሔር ሰዎችን ይጣራል። ይህ ለእነርሱ፣ “ጥሪ” ነው።
|
|
* መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “መጠራት” የሚለው ቃል የእርሱ ልጆች እንዲሆኑ፣ በኢየሱስ በኩል የሚገኘውን የመዳን መልእክት የሚናገሩ አገልጋዮቹ እንዲሆኑ እግዚአብሔር ሰዎችን መሾሙን ወይም መምረጡን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።
|
|
* ይህ ቃል ለአንድ ሰው ስም ማውጣትን በተመለከተም ጥቅም ላይ ይውላል። “ዮሐንስ ተባለ” ሲባል፣ “ዮሐንስ ተብሎ ተጠራ” ወይም “የእርሱ ስም ዮሐንስ ሆነ” ማለት ነው።
|
|
* “በአንድ ሰው ስም መጠራት” ማለት ለአንድ ሰው የሌላው ሰው ስም ተሰጠው ማለት ነው። እግዚአብሔር ሕዝቡን በራሱ ስም እንደ ጠራ ይናገራል።
|
|
* “በስሜ ጠርቻችኋለሁ” የተሰኘው የተለየ ሐረግ እግዚአብሔር ሰውን በግል በስሙ ያውቀዋል በተለየ ሁኔታም መርጦታል ማለት ነው።
|