am_tw/bible/other/written.md

1006 B

የተጻፈ

“እንደ ተጻፈ” ወይም፣ “የተጻፈው” የተሰኙት ቃሎች አዲስ ኪዳን ውስጥ ተደጋግመው ጥቅም ላይ ውለዋል፣ ብዙውን ጊዜ የሚያመለክቱት በዕብራውያን ቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፉ ትእዛዞች ወይም ትንቢቶች ነው።

  • አንዳንዴ፣ “እንደ ተጻፈ” የሚለው የሚያመለክተው በሙሴ ሕግ ውስጥ የተጻፉ ነገሮችን ነው።
  • ሌላ ጊዜ ደግሞ፣ ከብሉይ ኪዳን ነቢያት አንዱን ለመጥቀስ ነው።
  • ይህም፣ “በሙሴ ሕግ እንደ ተጻፈ” ወይም፣ “ከብዙ ዘመን በፊት ነቢያት እንደ ጻፉት” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።
  • ሌላ ጊዜ ደግሞ፣ “እንደ ተጻፈ” የሚለውን መተርጎምና ያ ምን ማለት እንደ ሆነ በግርጌ ማስታወሻ ማመልከት ሌላው አማራጭ ሊሆን ይችላል።