1.3 KiB
1.3 KiB
ማበራየት፣ ማበጠር
“ማበራየት” እና፣ “ማበጠር” ለምግብ የሚሆነውን እህል ከማይፈልጉ ነገሮች መለየት ማለት ነው። ስሞችን መለየትን ወይም መክፈልን አስመልክቶ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁለቱም ቃሎች በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ውለዋል።
- ማበራየት ነፋስ ገለባውን እንዲወስደው እህሉንና ገለባውን ወደ አየር በመበተን እህልን ከማይፈለገው ገለባ መለየት ማለት ነው።
- “ማበጠር” የሚባለው ድንጋይን ጠጠርን የመሳሰሉ የማይፈለጉ ነገሮች ከእህሉ እንዲለዩ የተበራየውን እህል በወንፊት ማበጠር ማለት ነው።
- ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ ጻድቃንን ከኀጢአተኞች የሚለይ አስቸጋሪ ሁኔታን ለማመልከት፣ “መበራየት” እና፣ “ማበጠር” የተሰኙት ቃሎች ጥቅም ላይ ውለዋል።
- እርሱንም ሆነ ሌሎች ደቀ መዛሙርት በእምነታቸው ፈተና እንደሚገጥማቸው ለማመልከት አንድ ጊዜ ኢየሱስ፣ “ማበጠር” በሚለው ቃል ተጠቅሞ ነበር።