am_tw/bible/other/water.md

1.7 KiB

ውሃ፣ ውሆች

ከመጀመሪያው ትርጕሙ በተጨማሪ፣ “ውሃ” - እንደ ውቅያኖስ፣ ባሕር፣ ሐይቅ ወይም ወንዝን የመሳሰሉ የውሃ አካል ይጨምራል።

  • “ወሆች” የሚለው የሚያመለክተው የውሃ አካላትን ወይም ብዙ የውህ ኣመገኛዎችን ነው። በጣም ስፋት ያለው ውሃን የሚያመለክት አጠቃላይ ቃል ሊሆንም ይችላል።
  • ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ፣ “ውሆች” ከባድ ችግርን፣ መከራንና አዳጋች ሁኔታን ያመለክታል። ለምሳሌ እግዚአብሔር በውሆች ውስጥ ብናልፍ እንኳ እንደሚጠብቀን ቃል ገብቷል።
  • “ብዙ ውሆች” የሚለው ሐረግ ችግሩ ምን ያህል ብዙ መሆኑን ያሳያል።
  • የቤት እንስሳትን፣ “ማጠጣት” ለእነርሱ ውሃ ማቅረብ ማለት ነው። መጥንት ዘመን ብዙውን ጊዜ እንዲህ የሚደረገው በመቅጃ ውሃ ከጉድጓድ በምቅዳትና እንስሶቹ እንዲጠቱ ገንዳ ላይ በማፍሰስ ነበር።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር ለሕዝቡ፣ “የሕያው ውሃ ምንጭ” እንደሆነ ተነግሯል። ይህም ማለት እርሱ የመንፈሳዊ ኀይልና ርካታ ሁሉ ምንጭ ነው ማለት ነው።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስ፣ “ሕያው ውሃ” የሚለውን ቃል የተጠቀመበት ለመለወጥና አዲስ ሕይወት ለማምጣት ሰው ውስጥ የሚሠራውን መንፈስ ቅዱስን ለማመልከት ነበር።