am_tw/bible/other/unclean.md

1.5 KiB

ንጹሕ ያልሆነ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ንሑሕ ያልሆነ” የሚለው ምሳሌያዊ አነጋገር የሚያመለክተው ሕዝቡ ሊነካው፣ ሊበላው ወይም መሥዋዕት ሊያቀርበው እንደማይገባው እግዚአብሔር የተናገረለት ነገርን ነው።

  • እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን የትኛው እንስሳ ንጹሕ፣ የትኛው እንስሳ ንጹሕ እንዳልሆነ መመሪያ ሰጥቷል። ንጹሕ ያልሆኑ እንስሳት እንዲበሉ ወይም መሥዋዕት እንዲቀርቡ አልተፈቀደም።
  • አንዳንድ ዐይነት የቆዳ በሽታ ያለባቸው ሰዎች ከዚያ እስኪፈወሱ ድረስ ንጹሕ እንዳልሆኑ ይቆጠሩ ነበር።
  • እስራኤላውያን ንጹሕ ያልሆነ ነገር ከነኩ ለተወሰነ ወቅት እነርሱ ራሳቸው ንጹሕ እንዳልሆኑ ይቆጠሩ ነበር።
  • ንጹሕ ያልሆነ ነገርን ባለመንካትና ባለመብላት ለእግዚአብሔር መታዘዝ እስራኤላውያንን ለእግዚአብሔር አገልግሎት የተለዩ ያደርጋቸው ነበር።
  • ይህ አካላዊና ሥርዓታዊ ንጹሕ አለመሆን፣ የግብረ ገባዊ ርኩሰት ምሳሌ ነበር።
  • በሌላ ምሳሌያዊ አነጋገር፣ “ንጹሕ ያልሆነ/ርኩስ” መንፈስ ክፉ መንፈስን ያመለክታል።