am_tw/bible/other/tentofmeeting.md

1.8 KiB

የስብሰባ ድንኳን

እግዚአብሔር በሲና ተራራ ሕጉን በሰጠ ጊዜ የስብሰባ ድንኳን እንዲሠሩ ለእስራኤላውያን ተናግሮ ነበር። ይህ ከእነርሱ ጋር የሚገናኝበት የተቀደሰ ቦታ ነበር። በምድረ በዳ በሚጓዙበት ጊዜ ይዘውት ይሄዱ ነበር፤ እግዚአብሔር ሲነግራቸው መልሰው ይተክሉት ነበር። * የስብሰባው ድንኳን የእንጨት ማዕቀፎች ላይ በተዘረጋ ጨርቅ የተሠራ ቤት ነበር።

  • የስብሰባውን ድንኳን ከጨርቅና ከእንጨት በተሠራ ግድግዳ በተከበበው ትልቅ አደባባይ መካከል እንዲተክሉ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ተናገረ።
  • መሠዊያውን አደባባዩ መካከል የስብስባው ድንኳን ፊት ለፊት እንዲያኖሩ እግዚአብሔር ነገራቸው። ሰዎች ወደ አደባባዩ በመሄድ ስቶታዎችንና መሥዋዕቶችን ለእግዚአብሔር ማቅረብ ይችላሉ። አገልግሎት ላይ ያሉ ካህናት ሰዎች ያመጡትን ይቀበሉና ሕጉ በሚጠይቀው መሠረት የመሥዋዕቱ መሠዊያ ላይ ያቀርቡታል።
  • የስብሰባው ድንኳን መካከሉ ላይ የተሰቀለ ወፍራም መጋረጃ ነበረው፤ ይህ መጋረጃ ድንኳኑን ለሁለት ይከፍለዋል። መጋረጃው ሰዎች በሌላው ወገን ያለውን ክፍል እንዳያዩና ወደዚያ እንዳይገቡ ይከልል ነበር። የመጀመሪያው ክፍል ቅድስት ይባላል፤ ወድዚያ የሚገቡ ካህናት ብቻ ነበር። ሁለተኛው ክፍል ቅድስተ ቅዱሳን ይባላል፤ ወደዚያ የሚገባው ሊቀ ካህናቱ ብቻ ነበር።