am_tw/bible/other/tencommandments.md

803 B

አሥሩ ትእዛዞች

እግዚአብሔር ለሙሴ እስራኤል ሊታዘዟቸው የሚገባ ብዙ ትእዛዞች ሰጥቶታል። ከእነዚህ ትእዛዞች አሥሩን በሁለት የድንጋይ ጽላቶች ላይ ጽፏቸዋል።

  • አሥሩ ትእዛዞች እስራኤላውያን እግዚአብሔርን እንዲወዱና እንዲያመልኩት፣ ሌሎች ሰዎችንም እንዲወዱ ለመርዳት የታሰቡ ልዩ ትእዛዞች ናቸው።
  • እነዚህ ትእዛዞች እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ያደረገው ኪዳን አካል ናቸው። እግዚአብሔር እንዲያደርጉ ለሰጣቸው ትእዛዝ ከታዘዙ እግዚአብሔርን መውደዳቸውንና የእርሱ መሆናቸውን ያሳያሉ።