am_tw/bible/other/tax.md

932 B

ቀረጥ ሰብሳቢ

የቀረጥ ሰብሳቢ ሥራ ከሰዎች የተቀበለውን ገንዘብ ለመንግሥት ማስተላለፍ ነበር

  • ኢየሱስና ሐዋርያቱ ባገለገሉበት ዘመን የሮም መንግሥት አይሁዳውያንን ቀረጥ ያስከፍል ነበር
  • ለሮም መንግሥት ቀረጥ ይሰበስቡ የነበሩ ሰዎች መንግሥት ከሚጠይቀው የበለጠ ገንዘብ ከሕዝቡ ይጠይቁ ነበር። ቀረጥ ሰብሳቢዎቹ ያንን ገንዘብ ለራሳቸው ይወስዱት ነበር
  • ሰዎችን በማታለላቸውና ለባዕዱ የሮም መንግሥት በመሥራታቸው አይሁድ ቀረጥ ሰብሳቢዎችን በጣም የባሰባቸው ኅጢአተኞች እንደሆኑ ይቆጥሩ ነበር። ለባዕድ መንግሥት መሥራታቸው የገዛ ሕዝባቸውን የካዱ አድርጓቸው ነበር