am_tw/bible/other/stiffnecked.md

1006 B

አንገተ ደንዳና፣ ግርት

“አንገተ ደንዳና” የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር ለእግዚአብሔር ባለ መታዘዝ የዳኑትንና ተግሣጹን የማይቀበሉ ሰዎችን ያመለክታል። እነዚህ ትዕቢተኞች ናቸው።

  • የመሲሑን መምጣት የነገሯቸውን ነቢያትን በተመለከተ ባሳዩት ዝንባሌ እስራኤላውያን አንገተ ደንዳና ሆነዋል
  • ሐሰተኛ አማልክትን በማምለክ በመቀጠላቸው እስራኤላውያን አንገተ ደንዳኖች መሆናቸው ታይቷል
  • ይህ ቃል፣ “በግትርነት የጸና” ወይም፣ “እብሪተኛና መመለስ የማይፈልግ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል
  • አንገተ ደንዳና ሰው ለእግዚአብሔር ሥልጣን አይገዛም
  • ሌሎች ቋንቋዎች ተመሳሳይ ትርጉም ያለው ፈሊጣዊ አነጋገር ሊኖራቸው ይችላል