am_tw/bible/other/splendor.md

1.0 KiB

ክብር

“ክብር” የሚለው ቃል ብዙ ጊዜ ከሀብትና መልክ ጋር የሚያያዝ የላቀ ውበትና ግርማ ያመለክታል

  • ብዙ ጊዜ፣ “ክብር” ጥቅም ላይ የሚውለው የሚያመለክተው አንድ ንጉሥ ያለውን ሀብት ወይም፣ የሚለብሳቸው ውድ ልብሶችና ውብ ቁመና ነው
  • ክብር የዛፎችና የተራሮችንና ሌሎች እግዚአብሔር የፈጠራቸው ነገሮችን ውበት ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል
  • አንዳንድ ከተሞች ያላቸው የተፈጥሮ ሃብት፣ ያማሩ ሕንፃዎች፣ መንገዶች፣ ውድ ልብሶችን፣ ወርቅና ብር ጨምሮ የሕዝቡን ሀብት ለማመልከት ክብር ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል
  • እንደ ዐውዱ አገባብ ይህ ቃል፣ “የላቀ ውበት” ወይም፣ “አስደናቂ ግርማ” ወይም፣ “ንጉሣዊ ታላቅነት” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል