am_tw/bible/other/snow.md

980 B

በረዶ

“በረዶ” ተራሮችን በመሳሰሉ ከፍታ ቦታዎች ወይም የዓለማችን ሰሜን ወይም ደቡብ ጫፍ ላይ የሚወርድ ውሃ አዘል ጠጣር ነገር ነው

  • በክረምት ኢየሩሳሌም ላይ በረዶ ይጥላል ሆኖም፣ ብዙ ጊዜ ሲጠራቀም አይታይም
  • ነጭ ነገርን ለማመልከት በረዶ እንደምሳሌ ይቀርባል
  • የበረዶ ንጣት የንፅሕና ሕይወት ተምሳሌት ነው
  • መጽሐፍ ቅዱስ፣ ኅጢአታችን እንደ በረዶ እንደሚነጣ ሲናገር እግዚአብሔር ሕዝቡን ፈጽሞ ከኅጢአታቸው ያነጻቸዋል ማለት ነው
  • የዮሐንስ ራዕይ የከበረው ክርስቶስን ሲያመለክትት፣ ጠጉሩ፣ “እንደበረዶ ነጭ” ነበር ይላል
  • አንዳንድ ቋንቋዎች በረዶን ለማመልከት የተለያዩ ቃሎች ይጠቀሙ ይሆናል