am_tw/bible/other/siege.md

847 B

መክበብ፣ ከበበ

“መክበብ” የሚለው ቃል አጥቂ ሰራዊት ከተማን ሲከብና ምግብም ሆነ መጠጥ ወደዚያ እንዳይገባ ማድረግን ያመለክታል። አንድን ከተማን መክበብ እንቅስቃሴዋን መቆጣጠር ማለት ነው

  • ባቢሎናውያን እስራኤልን ለማጥቃት በመጡ ጊዜ ከተማው ውስጥ ያለውን ሕዝብ ለማዳከም ኢየሩሳሌምን ከበቡ
  • ከበባ በሚደረግበት ጊዜ ወደ ከተማዋ ቅጥሮች መሻገርና ከተማዋን መቆጣጠር እንዲችል ወራሪው ሰራዊት ቀስ በቀስ ዙሪያውን ካብ ይሠራ ነበር
  • “ከበባ ውስጥ” የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር የጠላት ጦር የከበባት ከተማን ያመለክታል