am_tw/bible/other/shield.md

960 B

ጋሻ

ጋሻ ከሚወረወር ፍላጻና ከሌሎችም ጠላት ከሚሰነዝራቸው ጥቃቶች ራሱን ለመከላከል አንድ ወታደር በጦርነት ይይዘው የነበረ ነገር ነበር ለአንድ ሰው ጋሻ መሆን እርሱን ከአደጋ መከለከል ማለት ነው

  • ጋሻዎች የተለያየ ቅርጽ ሊኖራቸው ቢችልም፤ አብዛኛውን ጊዜ ግን ክብ ወይም ሞላላ ናቸው
  • ጋሻዎች የሚሠሩት ቆዳን፣ እንጨትን ወይም ሰይፍ፣ ጦርና ፍላጻን መቋቋም በሚችል ብረት ነው
  • ይህን ቃል እንደተለዋጭ ዘይቤ በመጠቀም፣ እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደሚከልል ጋሻ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ያመለክታል
  • ጳውሎስም፣ አማኞችን ከመንፈሳዊ ጥቃትና ከሰይጣን ስለሚከልል፣ “የእምነት ጋሻ” ተናግሮአል