am_tw/bible/other/sheep.md

1.1 KiB

በግ፣ አውራ፣ እንስት በግ

በግ አካሉ ላይ የሱፍ መሥሪያ ጠጉር ያለው መጠነኛ ቁመት ያለው ባለአራት እግር እንስሳ ነው። ወንዱ በግ አውራ ሲባል ሴቷ እንስት በግ ትባላለች

  • እስራኤላውያን አብዛኛውን ጊዜ መሥዋዕት የሚያቀርቡት በግ በተለይም ወንዱንና ከግልገል ከፍ ያለውን በግ ነበር
  • ሰዎች የበጎችን ሥጋ ይመገባሉ፤ ጠጉራቸውን ሱፍና ሌሎች ነገሮችን ለመሥራት ይጠቀሙበታል
  • በግ ሌሎችን የሚያምኑ፣ ደካማና ድንጉጦች ናቸው። በቀላሉ ከቦታቸው የሚኮበልሉ ናቸው። በትክክለኛው አቅጣጫ የሚመራቸው፣ የሚከለከልላቸውና ምግብ፣ ውሃና መጠለያ የሚያዘጋጅላቸው እረኛ ያስፈልጋቸዋል
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰዎች የእግዚአብሔር እረኝነት በሚያስፈልጋቸው በጎች ተመስለዋል