am_tw/bible/other/seed.md

1.1 KiB

ዘር

ዘር እርሱን የመሳሰሉ ብዙ ዘሮች እንዲገኙ መሬት ላይ የሚዘራ ወይም የሚተከል የአትክልት ክፍል ነው። በርካታ ምሳሌያዊ ትርጉሞችም አሉት

  • “ዘር” የሚለው ቃል ሕፃን ሴት ማሕፀን ውስጥ እንዲፈጠር ወንድ ወይም ሴት ውስጥ ያለውን ፍሬ ለማመልከት ጥቅም ላይ የሚውል ምሳሌያዊ ቃል ነው
  • ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ “ዘር” የአንድን ሰው ልጆች ወይም ዘሮች ሊያመለክትም ይችላል
  • ይህ ቃል ከአንድ የበለጠ ዘር ወይም ከአንድ የበለጠ ትውልድ ለማመልከት ብዙ ጊዜ ሁለት ትርጉሞች ይኖሩታል
  • ኢየሱስ ስለ ዘሪው በተናገረው ምሳሌ ዘር መልካም መንፈሳዊ ፍሬ እንዲያፈራ ሰውልብ ውስጥ ከሚተከል የእግዚአብሔር ቃል ጋር ተመሳስሎአል
  • ሐዋርያው ጳውሎስም የእግዚአብሔርን ቃል ለማመልከት፣ “ዘር” በተሰኘው ቃል ተጠቅሟል