am_tw/bible/other/province.md

810 B

አውራጃ

አውራጃ አንድ ወረዳ ወይም የአገር ክፍል ነው።

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ አውራጃዎች በንጉሥ አክዓብና በአስቴር ዘመን የእስራኤል ክፍሎች ነበሩ።
  • አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን የሮም መንግሥት በተለያዩ አውራጃዎች የተከፋፈለ ነበር፤ ከእነርሱም መካከል መቄዶንያ፣ ቆጵሮስ፣ እስያ፣ ሶርያ፣ ግብፅና ገላትያ ይገኙ ነበር።
  • እያንዳንዱ አውራጃ የራሱ ገዢ የነበሩት ሲሆን፣ እርሱም ለንጉሡ ወይም ለአገሩ አስተዳደር ይገዛ ነበር።
  • ይህ ቃል፣ “አካባቢ” ወይም፣ “ክልል” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።