am_tw/bible/other/plead.md

923 B

መለመን፣ ልመና

“መለመን” አንድ ነገር እንዲደረግ ወይም እንዲሰጥ አጥብቆ መጠየቅ ማለት ነው። “ልመና” የሚለው የሚያመለክተው የመለመንን ተግባር ነው።

  • ብዙውን ጊዜ ልመናያ ሰው ከባድ ችግር ውስጥ መሆኑን ወይም እግዚአብሔር አንድን ሰው እንዲረዳ አጥብቆ መፈለግን ያመለክታል።
  • ምሕረት እንዲደረግላቸው ወይም ጉዳያቸው ፍርድ እንዲያገኝላቸው ሰዎች ንጉሥን ወይም ገዢን ይለምናሉ።
  • ይህን ቃል ለመተርጎም፣ “መጠየቅ” ወይም. “መወትወት” የተሰኙ ቃሎችም ያገለግላሉ።
  • “መለመን” የሚለውን ቃል፣ “አስቸኳይ ጥያቄ” ወይም፣ “አጥብቆ ማሳሰብ” ማለትም ይቻላል።