am_tw/bible/other/pierce.md

832 B

መውጋት

“መውጋት” ስለት ባለው ሹል ነገር መውጋት ማለት ሲሆን፣ ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ሰውን በጣም ማሳዘንን ለማመልከትም ጥቅም ላይ ይውላል።

  • ኢየሱስ መስቀል ላይ ተሰቅሎ እያለ አንድ ወታደር ጎኑን በጦር ወጋው።
  • ከመጽሐፍ ቅዱስ እንደምንመለከተው አንድ ባርያ ነጻ ሲወጣና ከጌታው ጋር ለመሆንና እርሱን ለማገልገል ለመምረጡ ምልክት እንዲሆን ጆሮውን ይወጋ (ይበሳ) ነገር።
  • ጦር ልቧን እንደሚወጋት ማለትም በልጇ በኢየሱስ ላይ ከሚደርሰው የተነሣ ከባድ ሐዘን እንደሚደርስባት ስምዖን ለማርያም ነግሯት ነበር።