am_tw/bible/other/partial.md

836 B

ማድላት፣ አድልዎ

“ማድላት እና፣ “አድልዎ” የተሰኙ ቃሎች፣ አንዳንድ ሰዎችን ከሌሎች የበለጠ ማቅረብ ወይም ከሌሎች የተለየ ነገር ማድረግን ያመለክታል።

  • ይህ ከአድሎአዊነት ጋር ይመሳሰላል፤ አድሎአዊነት ሰዎች ሀብታም ወይም የተሳካላቸው ስለሆኑ ብቻ ለሌሎች የማናደርገውን ለእነርሱ ማድረግ ማለት ነው።
  • ሀብት ላላቸው ወይም ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ላሉ ሰዎች እንዳናደላ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል።
  • ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ እግዚአብሔር ያለ ምንም አድልዎ ለሰዎች በቅንነት እንደሚፈርድ ይናገራል።