am_tw/bible/other/palm.md

703 B

ዘንባባ

“ዘንባባ” ረጃጅም፣ በቀላሉ የሚተጣጠፍ፣ ከጫፉ ጀምሮ እንደማራገቢያ ዓይነት ቅጠል ያበዛባቸው ቅርንጫፎች ያሉት ረጅም የዛፍ ዘር ነው።

  • አብዛኛውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገርለት “ቴምር” የሚባል ፍሬ ስለሚያፈራው የዘንባባ ዛፍ ነው።
  • ኢየሱስ በአህያ ተቀምጦ ኢየሩሳሌም ሲገባ ሰዎቹ እርሱ ፊት መሬቱ ላይ የዘንባባ ዝንጣፊ አንጥፈው ነበር።
  • የዘንባባ ቅርንጫፎች(ዝንጣፊዎች) ሰላምንና የድል መታሰቢያን ያመለክታትሉ።