am_tw/bible/other/multiply.md

818 B

መብዛት

“መብዛት” የሚለው በከፍተኛ ደረጃ በቁጥርና በመጠን ማደግን ያመለክታል።

  • “እንዲበዙ” እና ምድርን እንዲሞሉ እግዚአብሔር ለሰው ልጆችና ለእንስሳት ተናግሮአል። ይህ በዐይነት እነርሱን የመሰሉትን እንዲወልዱየተሰጠ ትእዛዝ ነው።
  • 5000 ሰዎችን መመገብ እንዲችል ኢየሱስ እንጀራዎቹና ዓሣዎቹ እንዲበዙ አደረገ። ሰው ሁሉ በልቶ እስኪጠግብ ድረስ የምግቡ መጠን መጨመሩን ቀጠለ።
  • ይህ ቃል፣ “በጣም መጨመር” ወይም፣ “በቁጥር ማደግ” ወይም፣ “ከቁጥር በላይ መሆን” ተብሎ መተርጎምም ይችላል።