am_tw/bible/other/manager.md

721 B

ኀላፊ፣ ባለ ዐደራ

መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ኀላፊ” ወይም “ባለ ዐደራ” የሚለው የጌታውን ንብረትና የሥራ እንቅስቃሴን በተመለከተ ሙሉ ኀላፊነት የተሰጠውን አገልጋይ ለማመልከት ነው።

  • ባለ አደራ በጣም ትልቅ ኀላፊነት የተሰጠው ሰው ሲሆን፣ ሌሎች አገልጋዮችን የመቆጣጠርንም ሥራ ይጨምራል።
  • ባለ አደራ ከሚለው ይልቅ፣ “ኀላፊ” የሚለው ይበልጥ በዘመኑ የተለመደ ቃል ነው፤ ሁለቱም የሚያመለክቱት የሌላው ሰው ተግባራዊ ጉዳዮችን ማስተዳደርን ነው።