am_tw/bible/other/lowly.md

693 B

ዝቅተኛ፣ ዝቅተኝነት

“ዝቅተኛ” እና፣ “ዝቅተኝነት” የተሰኙት ቃሎች ድህነትን ወይም ዝቅ ያሉ ማንነትና ደረጃን ያመለክታሉ።

  • ኢየሱስ ሰው ወደ መሆንና ባርያ ወደ መሆን ደረጃ ድረስ ራሱን ዝቅ አደረገ።
  • እርሱ የተወለደው ቤተ መንግሥት ሳይሆን የከብቶች ማደሪያ በረት ውስጥ ስለ ነበር ልደቱም በጣም ዝቅተኛ ነበር።
  • ዝቅተኛ ለሚለው ሌላው ቃል፣ “ትሑት” የሚለው ሊሆን ይችላል።
  • ዝቅተኛ ዝንባሌ የትዕቢተኝነት ተቃራኒ ነው።