am_tw/bible/other/light.md

1.7 KiB

ብርሃን

መጽሐፍ ቅዱስ “ብርሃን” የሚለውን ቃል በተለያዩ ምሳሌያዊ ገለጻዎች ይጠቀምበታል። ብዙውን ጊዜ ጻድቃን፣ ቅድስናንና እውነትን ለማመልከት እንደ ተለዋጭ ዘይቤ ያገለግላል።

  • የእግዚአብሔርን እውነተኛ መልእክት ወደ ዓለም ማምጣቱንና ሕዝቡንም ከጨለማና ከኀጢአት እንደሚያድን ለማመልከት ኢየሱስ፣ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ” አለ።
  • ክርስቲያኖች “በብርሃን እንዲመላለሱ” ታዝዘዋል፤ ያም ማለት እግዚአብሔር በሚፈልገው መንገድ መኖርና ክፋትን ማስወገድ አለባቸው ማለት ነው።
  • ሐዋርያው ዮሐንስ፣ “እግዚአብሔር ብርሃኝ” እንደ ሆነና በእርሱ ጨለማ እንደሌለ ጽፏል።
  • ብርሃንና ጨለማ ፍጹም ተቃራኒ ናቸው። ጨለማ ምንም ዐይነት ብርሃን ያለ መኖር ማለት ነው።
  • እርሱ፣ “የዓለም ብርሃን” እንደ ሆነና ተከታዮቹም እግዚአብሔር ምንኛ ታላቅ መሆኑን በሚያሳይ መንገድ እየኖሩ በዓለም ውስጥ እንደ ብርሃን ማንጸባረቅ እንደሌለባቸው ኢየሱስ ተናግሮአል።
  • “በብርሃን መመላለስ” መልካምና ትክክል የሆነውን በማድረግ እግዚአብሔርን ደስ በሚያሰኝ መንገድ መኖርን ይወክላል። በጨለማ መመላለስ በእግዚአብሔር ላይ እያመፁ መኖርንና ክፉ ነገሮችን ማድረግን ይወክላል።