am_tw/bible/other/lampstand.md

666 B

መብራት መያዣ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “መብራት መያዣ” ክፍሉ ውስጥ ሁሉ እንዲያበራ መብራቱ የሚቀመጥበት ከእንጨት ወይም ከብረት የተሠራ ዕቃ ነው።

  • ለቤተ መቅደሱ የሚሠራው ልዩ መብራት መያዣ ሰባት መብራቶች የሚይዙበት ቦታ ነበሩት።
  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን መብራት ብዙውን ጊዜ የወይራ ዘይት ወይም ስብ የያዘ ከሸክላ የተሠራ ዕቃ ሲሆን ሲቀጣጠል ብርሃን የሚሰጥ ክር ወይም ፈትል ውስጡ ይደረግ ነበር።