am_tw/bible/other/joy.md

1.0 KiB

ደስታ፣ ደስተኛ

ደስታ የደስታ ስሜት ወይም ከእግዚአብሔር የሚመጣ ጥልቅ ርካታ ነው። ከዚሁ ጋር ታያያዥ የሆነው፣ “ደስተኛ” የሚለው ቃል በጣም ደስ የተሰኘ ሰውን ያመለክታል።

  • እያለፈበት ያለው መልካም መሆኑን በተመለከተ ጥልቅ ግንዛቤ ሲኖረው አንድ ሰው ደስታ ይሰማዋል።
  • ለሰዎች እውነተኛ ደስታ የሚሰጥ እግዚአብሔር ነው።
  • ደስ ለመሰኘት የግድ ደስ የሚል አካባቢ ወይም ሁኔታ ውስጥ መሆን የለብንም በሕይወታቸው በጣም አስቸጋሪ ነገሮች እየተፈፀሙ እንኳ እግዚአብሔር ለሰዎች ደስታ መስጠት ይችላል።
  • አንዳንዴ ቤቶችን ወይም ከተሞችን የመሳሰሉ ነገሮች ደስ የሚያሰኙ ተብለዋል። እንዲህም ማለት እዚያ የሚኖሩ ሰዎች ደስተኞች ናቸው ማለት ነው።