am_tw/bible/other/jewishleaders.md

1.2 KiB

የአይሁድ መሪዎች፤ የአይሁድ ባለ ሥልጣኖች፣ የሃይማኖት መሪዎች

የአይሁድ መሪዎች ካህናትንና የሕግ ምሑራንን የመሳሰሉ የሃይማኖት መሪዎች ነበሩ።

  • ብዙዎቹ የሃይማኖት መሪዎች ኢየሱስ መሲሕ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን አላመኑበትም። በኢየሱስ ላይ ቅናት ስላደረባቸው ሌሎችም ቢሆኑ በእርሱ እንዲያምኑ አልፈለጉም።
  • አንዳንድ የሃይማኖት መሪዎች መሞት ከተነሣ በኋላ እንኳ በኢየሱስ አላመኑም።
  • ብዙዎቹ የሃይማኖት መሪዎች ከሌሎች ይልቅ እነርሱ ጻድቃን እንደሆኑ ያስቡ ነበር፤ ኀጢአተኛ መሆናቸውን እንዳይቀበሉም ትዕቢት ነበራቸው። ኢየሱስን አስመልክቶ ለሮማውያን ሐሰት ተናግረው እርሱ እንዲገደል ጠየቁ።
  • ኢየሱስ የአይሁድ መሪዎችን ግብዝነት አወገዘ። እግዚአብሔርን እንደሚያውቁ ይናገራሉ፤ ግን ለእርሱ አይታዘዙም።