1.2 KiB
1.2 KiB
የአይሁድ መሪዎች፤ የአይሁድ ባለ ሥልጣኖች፣ የሃይማኖት መሪዎች
የአይሁድ መሪዎች ካህናትንና የሕግ ምሑራንን የመሳሰሉ የሃይማኖት መሪዎች ነበሩ።
- ብዙዎቹ የሃይማኖት መሪዎች ኢየሱስ መሲሕ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን አላመኑበትም። በኢየሱስ ላይ ቅናት ስላደረባቸው ሌሎችም ቢሆኑ በእርሱ እንዲያምኑ አልፈለጉም።
- አንዳንድ የሃይማኖት መሪዎች መሞት ከተነሣ በኋላ እንኳ በኢየሱስ አላመኑም።
- ብዙዎቹ የሃይማኖት መሪዎች ከሌሎች ይልቅ እነርሱ ጻድቃን እንደሆኑ ያስቡ ነበር፤ ኀጢአተኛ መሆናቸውን እንዳይቀበሉም ትዕቢት ነበራቸው። ኢየሱስን አስመልክቶ ለሮማውያን ሐሰት ተናግረው እርሱ እንዲገደል ጠየቁ።
- ኢየሱስ የአይሁድ መሪዎችን ግብዝነት አወገዘ። እግዚአብሔርን እንደሚያውቁ ይናገራሉ፤ ግን ለእርሱ አይታዘዙም።