am_tw/bible/other/house.md

1.2 KiB

ቤት

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ፣ “ቤት” ጥቅም ላይ የዋለው በምሳሌያዊ መልኩ ነው።

  • አንዳንዴ፣ አንድ ቤት ውስጥ አብሮ የሚኖሩ ሰዎችን የምያመለልክት፣ “ቤተ ሰብ” እንደ ማለት ይሆናል።
  • ብዙ ጊዜ፣ “ቤት” የአንድን ሰው ቅድመ አባቶች፣ ዘሮች ወይም ዘመዶች ያመለክታል፤ ለምሳሌ፣ “የዳዊት ቤት” እንደሚለው።
  • “የእግዚአብሔር ቤት” እና፣ “የያህዌ ቤት” የተሰኘው ሐረግ መገናኛውን ድንኳን ወይም ቤተ መቅደስን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል። በጠቅላላው እግዚአብሔር ያለበትን ወይም የሚኖርበትን የሚያመለክት ሊሆን ይችላል።
  • ዕብራውያን 3 ላይ፣ “የእግዚአብሔር ቤት” ሲል እንደ ተለዋጭ ዘይቤ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ወይም የበለጠ ጠቅለል ባለ መልኩ መላውን የእስራኤልን ሕዝብ ወይም በሰሜናዊው የእስራኤል መንግሥት ያሉ ነገዶችን ለይቶ ማመልከቱ ነው።