am_tw/bible/other/horse.md

926 B

ፈረስ

ፈረስ ግዙፍ ባለ አራት እግር እንስሳ ሲሆን፣ መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን በአብዛኛው ለእርሻ ሥራና ለሰዎች መጓጓዣ ያገለግል ነበር።

  • አንዳንድ ፈረሶች ሰረገላና ጋሪ ለመጎተት ሲያገለግሉ፣ ሌሎች ሰዎችን በመሸከም ያገለግሉ ነበር።
  • ወደ ተፈለገው አቅጣጫ ፈረሶችን መምራት እንዲቻል አፋቸው ውስጥ ልጓም ይገባል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን በአመዛኙ በጦርነት ጊዜ ካላቸው ጠቀሜታ የተነሣ ፈረሶች እንደ ትልቅ ሀብት የባለጠጋነት መለኪያ ይቆጠሩ ነበር። ለምሳሌ ንጉሥ ሰሎሞን አንድ ሺህ ፈረሶች ነበሩት።
  • ፈረስ የሚመስሉ እንስሳት አህያና በቅሎ ናቸው።