am_tw/bible/other/horn.md

1.2 KiB

ቀንድ፣ ቀንዶች

ቀንዶች ላምና በሬ፣ በጎችና ፍየሎች የመሳሰሉ እንስሳት ራስ ላይ የሚበቅል ቋሚና ሹል ነገር ነው። ብርታትን፣ ኀይልን፣ ሥልጣንና ንጉሥነትን ለማመልከትም “ቀንድ” በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።

  • የበግ ቀንድ በአንዳንድ ሃይማኖታዊ ክብረ በዓላት ጊዜ የሚነፋውን፣ “ሸፋር” የተሰኙ የሙዚቃ መሣሪያ መሥሪያ ይሆናል።
  • ከናስ የተሠራው የዕጣን መሠዊያ ላይ በአራቱም አቅጣጫ የቀንድ ቅርጽ ያለው ነገር እንዲያደርጉ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ተናግሮአል። እነዚህ ነገሮች “ቀንዶች” ተብለው ቢጠሩም ትክክለኛ የእንስሳት ቀንዶች አልነበሩም።
  • ውሃ ወይም ዘይት ለመያዣ የሚያገለግለው ቀንድ መሰል ብልቃጥ አንዳንዴ፣ “ቀንድ” ተብሎ ይጠራል። የዘይት ብልቃጥ ሳሙኤል ዳዊት ላይ እንዳደረገው አንድን ንጉሥ ለመቀባት ያገለግላል።