am_tw/bible/other/highplaces.md

1021 B

ከፍታ ቦታዎች

“ከፍታ ቦታዎች” የሚለው ሐረግ የጣዖት አምልኮ መሠዊያና ማምለኪያ ቤት የሚሠራባቸው ኮረብቶች ወይም ተራሮች ላይ ያሉ ቦታዎችን ያመለክታል።

  • በእነዚህ ከፍታ ቦታዎች ለሐሰተኛ አማልክት መሠዊያዎች በመሥራት ብዙዎቹ የእስራኤል ንጉሦች እግዚአብሔርን በድለው ነበር። ይህም ሕዝቡ በከፍተኛ ደረጃ ጣዖት እንዲያመልኩ አደረገ።
  • እግዚአብሔርን የሚፈራ ንጉሥ በእስራኤል በነገሠ ጊዜ ሁሉ ከፍታ ቦታዎችን ያስወግድና ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ነበር።
  • ይሁን እንጂ፣ ከእነዚህ መልካም ንጉሦች አንዳንዶቹ ቸልተኛ ነበሩ፤ መላው የእስራኤል ሕዝብ ጣዖት ማምለኩን እንዲቀጥል ምክንያት የሆኑትን ከፍታ ቦታዎች አላስወገዱም።