1.8 KiB
1.8 KiB
ራስ
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ራስ” በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞች አሉት።
- ብዙውን ጊዜ ይህ ቃል ሰዎች ላይ ባለ ሥልጣን መሆንን ያመለክታል፤ ለምሳሌ፣ “በሕዝቦች ላይ ራስ አደረግኸኝ” እንደሚለው ይህ፣ “የሕዝቦች መሪ አደረግኸኝ” ወይም፣ “ሥልጣን ሰጠኸኝ” ተብሎ መተርጎም ይችላል።
- ኢየሱስ፣ “የቤተ ክርስቲያን ራስ” ተብሏል። የሰው ራስ የሰውነት ብልቶቹን እንደሚምራና አቅጣጫ እንደሚያስይዝ ሁሉ ኢየሱስም “የአካሉን” ማለትም የቤተ ክርስቲያን ብልቶች (አባሎች) ይመራል፤ አቅጣጫ ያስይዛል።
- ባል የሚስቱ ራስ ወይም ባለ ሥልጣን መሆኑን አዲስ ኪዳን ያስተምራል። ሚስቱንና ቤተሰቡ የመምራትና አቅጣጫ የማስያዝ ኀላፊነት ተሰጥቶታል።
- “በራሱ ላይ ምላጭ አያልፍም” የሚለው አገላለጽ፣ “ጠጉሩ አይቆረጥም ወይም አይላጭም” ማለት ነው።
- “ራስ” የአንድን ነገር ጅማሬ ወይም ምንጭ ሊያመለክትም ይችላል፤ ለምሳሌ፣ “የመንገዱ ራስ” እንደሚለው።
- ሰውየውን ሽማግሌ ነው ለማለት የሰውየው “ራሱ ግራጫ ነው” ሲባል ራሱን ብቻ ሳይሆን ሙሉውን ሰው ይወክላል፤ “የዮሴፍ ራስ” ዮሴፍን ያመለክታል።
- “ደማቸው በራሱ ላይ ይሁን” ሲባል ለእነርሱ ሞት ኀላፊነቱን ይወስዳል፤ በዚያም ምክንያት ይቀጣል ማለት ነው።