am_tw/bible/other/firstfruit.md

1.1 KiB

በኩራት

“በኩራት” የሚለው ቃል የሚያመለክተው በእያንዳንዱ መከር ወቅት ከሚሰበሰበው እህል ሆነ አትክልት የመጀመሪያውን ፍሬ ነው።

  • የስጦታ መሥዋዕት እንደሆነ እስራኤላውያን ለእግዚአብሔር በኩራት ያቀርቡ ነበር።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ቃሉ ቤተሰቡ ውስጥ የሚወለደውን የመጀመሪያ ወንድ ልጅ ለማመልከት ምሳሌያዊ በሆነ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል። ያም ማለት የቤተሰቡ የመጀመሪያ ልጅ እንደመሆኑ መጠን፣ የቤተሰቡ ስም እና ክብር የሚጠራው በእርሱ ነው ማለት ነው።
  • ኢየሱስ ከሞት በመነሣቱ ለሞቱትና አንድ ቀን ከሞት ለሚነሡት አማኞች ሁሉ፣ “በኩራት” ነው ብሎአል።
  • በኢየሱስ የሚያምኑ አማኞችም፣ የፍጥረታቱ በኩራት ተብለዋል፤ ይህ የሚያመለክተው ኢየሱስ ያዳናቸው ሕዝቡ እንዲሆኑ የጠራቸው ያላቸውን መብትና ቦታ ነው።