am_tw/bible/other/firstborn.md

1.1 KiB

በኩር

“በኩር” የሚለው ቃል መጀመሪያ የሚወለደውን የሰውም ሆነ የእንስሳትን የመጀመሪያ ልጅ ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ “በኩር” የሚያመለክተው መጀመሪያ የሚወለድ ወንድ ልጅን ነው።
  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የበኩር ልጅ ሌሎች ልጆች የሚያገኙትን የቤተሰብ ዕጥፍ የመውረስ መብት ነበረው።
  • ብዙውን ጊዜ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት የሚቀርበው መጀመሪያ የተወለደው እንስሳ ነበር።
  • ይህ ቃል ምሳሌያዊ በሆነ መልኩም ጥቅም ላይ ይውላል። ለምሳሌ ከሌሎች ሕዝቦች የተለየ መብት ስለሰጣቸው የእስራኤል ሕዝብ የእግዚአብሔር በኩር ተብለው ተጠርተው ነበር።
  • በሌሎች ሁሉ ላይ ባለው ሥልጣንና የበላይነት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስም “በኩር” ተብሏል።