am_tw/bible/other/fellowshipoffering.md

852 B

የኅብረት መሥዋዕት፣ የሰላም መሥዋዕት

የኅብረት መሥዋዕት ብሉይ ኪዳን ውስጥ የሰላም መሥዋዕት ተብሎ ይጠራል። ተባዕት ወይም እንስት እንስሳ መሥዋዕት የሚቀርብበት ነው።

  • ይህ መሥዋዕት ከሚቀርብበት ምክንያቶች ጥቂቶቹ፣ ስእለትን ለመፈጸም፣ ለእግዚአብሔር ምስጋናና ውዳሴ ለማቅረብ፤
  • የመሥዋዕቱ የተወሰነው ክፍል ለእግዚአብሔር ከቀረበ በኋላ የኅብረቱን መሥዋዕት ካህናቱ፣ መሥዋዕቱን ያመጣው ሰው እና ሌሎች እስራኤላውያን ይከፋፈሉታል።
  • ከዚህ መሥዋዕት ጋር ያልቦካ እንጀራንም የሚያካትት አብሮ መብላትም ይኖራል።