am_tw/bible/other/family.md

1021 B

ቤተሰብ

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቤተሰብ በዚህ ዘመን፣ “የሩቅ” ቤተሰብ የምንለውን ጨምሮ በጋብቻ ወይም በመወለድ የተዛመዱ ሰዎች መኅበረሰብ ነው።

  • የአይሁድ ቤተሰብ በአምልኮና በአስተምህሮ አማካይነት ከአንዱ ወደሌላው የሚተላለፍ ባሕል ያለው ሃይማኖታዊ ማኅበረሰብ ነው።
  • ብዙውን ጊዜ የቤተሰቡ ዋና ባለሥልጣን የሚሆነው አባት ነው።
  • ቤተሰብ ሲባል፣ አገልጋዮችን፣ የሩቅ ዘመዶችን ሌላው ቀርቶ ቤት ውስጥ ያሉ ባዕድ ሰዎችንም ያካትታል።
  • አንዳንድ ቋንቋዎች “ነገድ” ወይም፣ “ጎሳ” የተሰኘ ሰፋ ያለ ቃል ይጠቀሙ ይሆናል፤ እየተናገረ ያለው ከወላጆችና ከልጆች ውጪ ስላሉት ከሆነ በዐውዱ መሠረት በእነዚህ ቃሎች መጠቀም ተገቢ ነው።