am_tw/bible/other/face.md

1.8 KiB

ፊት

“ፊት” የሚለው ቃል የአንድ ሰው ራሱ ከፊት በኩል ያለውን ክፍል ነው፤ ቃሉ አያሌ ምሳሌያዊ ትርጉሞች አሉት።

  • “ፊትህ” ማለት፣ “አንተ” ማለት ሲሆን፣ በተመሳሳይ፣ “ፊቴ” ማለት፣ “እኔ” ወይም፣ “የእኔ” ማለት ነው።
  • አንድ ሰው ወይም አንድን ነገር፤ “ፊት ለፊት” መግጠም ማለት በቀጥታ ያን ሰው ወይም ነገር ወዳለበት አቅጣጫ መመልከት ማለት ነው።
  • “ፊት ለፊት መገናኘት” ማለት፣ “ፊት ለፊት መተያየት” ማለት ነው።
  • “ፊት ለፊት መሆን” ሁለት ሰዎች በቅርብ ርቀት እርስበርስ ሲተያዩ ማለት ነው።
  • ኢየሱስ፣ “ወደኢየሩሳሌም ለመሄድ ፊቱን አቀና” ማለት ወደዚያ ለመሄድ ወሰነ ማለት ነው።
  • አንድ ሰው ወይም አገር ላይ፣ “ፊትን ማክበድ” ላለመርዳት መወሰን ወይም ያን ሰው ወይ አገር ችላ ማለት ማለት ነው።
  • “የምድሪቱ ፊት” የሚለው ሐረግ የምድሪቱን ውጫዊ ገጽታ የሚያመለክት ሲሆን ብዙውን ጊዜ፣ ምድርን ሁሉ የሚያመለክት አጠቃላይ ቃል ነው። ለምሳሌ፣ “የምድርን ፊት የሚሸፍን ራብ” ሲባል፣ ብዙ ሰዎችን ጉዳት ላይ የጣለ ራብ መስፋፋቱን ነው የሚያመለክተው።
  • “ከሕዝብህ ፊትህን አትሰውር” የሚለው ምሳሌያዊ አገላለጽ፣ “ሕዝብህን ችላ አትበል” ወይም፣ “ሕዝብህን አትተው” ወይም፣ “ለሕዝብህ ማሰብን አትተው” ማለት ነው።