am_tw/bible/other/endure.md

775 B
Raw Blame History

መታገሥ፣ ትዕግሥት (ጽናት)

መታገሥ ረጅም ጊዜ መቆየት ወይም አስቸጋሪ ነገርን መቋቋም ማለት ነው።

  • የፈተና ጊዜ ሲመጣ ተስፋ ሳይቆርጡ ጸንቶ መቆም ማለትም ነው።
  • “መታገሥ - “መቻል” “በመከራና ስደት ውስጥ መጽናት” ማለት ነው።
  • “እስከ መጨረሻ ጽኑ” በማለት ለክርስቲያኖች የተሰጠው ማበረታቻ ምንም እንኳ ያንን ማድረጋቸው ከባድ መከራ ሊያመጣባቸው ቢችልም ለኢየሱስ መታዘዝ እንደሚገባቸው ያሳስባቸዋል።
  • “መከራን መታገሥ” ሲባል፣ “መከራን መለማመድ” ማለትም ነው።