am_tw/bible/other/elder.md

1.3 KiB

ሽማግሌ

ሽማግሌዎች በእግዚአብሔር ሕዝብ መሐል መንፈሳዊና ተግባራዊ መሪነት ኀላፊነት ያላቸው መንፈሳዊ ማስተዋል ያላቸው ስሞች ናቸው።

  • መጀመሪያ ላይ ይህ ቃል የተወሰደው ሽማግሌዎቹ የሚሆኑት በዕድሜያቸውና በሕይወት ልምዳቸው ከወጣቶች ይልቅ አስተዋይ የሆነ ስምች ስለ ነበሩ ነው።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሽማግሌዎች ማኅበራዊ ፍትሕንና የሙሴ ሕግን በተመለከተ እስራኤላውያን በመምራት ያገለግሉ ነበር።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ የአይሁድ ሽማግሌዎች ማኅበረ ሰባቸውንና በመምራትና ሕዝባቸውን በመዳኘት ቀጥለው ነበር።
  • በጥንት ቤተ ክርስቲያን ክርስቲያን ሽማግሌዎች በየአካባቢው በነበረ የአማኞች ጉባኤ መንፈሳዊ አመራር ይሰጡ ነበር።
  • መንፈሳዊ ማስተዋል ያላቸው ወጣቶችም የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች ይሆኑ ነበር።
  • ይህ ቃል፣ “በዕድሜ የገፉ ሰዎች” ወይም፣ “ቤተ ክርስቲያንን የሚመሩ መንፈሳዊ ማስተዋል ያላቸው ሰዎች” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።