am_tw/bible/other/eagle.md

1.0 KiB

ንስር

ንስር እንደ ዓሣ፣ አይጥ፣ እባብና ጫጩት የመሳሰሉ ትንንሽ እንስሳትን የሚመገብ በጣም ግዙፍና ብርቱ ወፍ ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ የሰራዊትን ፍጥነትና ብርታት ንስር የሚመገበውን እንስሳ በፍጥነትና በድንገት ነጥቆ ከሚወስድበት ሁኔታ ጋር ያመሳስላል።
  • በእግዚአብሔር የሚተማመኑ እንደ ንስር ወደ ላይ እንደሚመጥቁ ኢሳይያስ ይናገራል። ይህ በእግዚአብሔር በመተማመንና ለእርሱም በመታዘዝ የሚገኘውን ነጻነትና ብርታት የሚያመለክት ምሳሌያዊ አነጋገር አንው።
  • ከትንቢተ ዳንኤል እንደምንመለከተው የንጉሥ ናቡከደነፆር ጸጉር ርዝመት ከንስር ላባዎች ጋር ተነጻጽሮአል፤ ይህም ከ50 ሳንቲ ሜትር የበለጠ ይረዝም ነበር ማለት ነው።